Main pages

Surah Competition [At-Takathur] in Amharic

Surah Competition [At-Takathur] Ayah 8 Location Maccah Number 102

أَلْهَىٰكُمُ ٱلتَّكَاثُرُ ﴿١﴾

በብዛት መፎካከር (ጌታችሁን ከመገዛት) አዘነጋችሁ፡፡

حَتَّىٰ زُرْتُمُ ٱلْمَقَابِرَ ﴿٢﴾

መቃብሮችን እስከ ጎበኛችሁ ድረስ፡፡

كَلَّا سَوْفَ تَعْلَمُونَ ﴿٣﴾

ተከልከሉ፤ ወደፊት (ውጤቱን) ታውቃላችሁ፡፡

ثُمَّ كَلَّا سَوْفَ تَعْلَمُونَ ﴿٤﴾

ከዚያም ተከልከሉ፤ ወደ ፊት ታውቃላችሁ፡፡

كَلَّا لَوْ تَعْلَمُونَ عِلْمَ ٱلْيَقِينِ ﴿٥﴾

በእውነቱ (የሚጠብቃችሁን) እርግጠኛ ዕውቀትን ብታውቁ ኖሮ፤ (ባልዘናጋችሁ ነበር)፡፡

لَتَرَوُنَّ ٱلْجَحِيمَ ﴿٦﴾

ገሀነምን በእርግጥ ታያላችሁ፡፡

ثُمَّ لَتَرَوُنَّهَا عَيْنَ ٱلْيَقِينِ ﴿٧﴾

ከዚያም እርግጠኛን ማየት ታዩዋታላችሁ፡፡

ثُمَّ لَتُسْـَٔلُنَّ يَوْمَئِذٍ عَنِ ٱلنَّعِيمِ ﴿٨﴾

ከዚያም ከድሎታችሁ ሁሉ በዚያ ቀን ትጠየቃላችሁ፡፡