Main pages

Surah The emissaries [Al-Mursalat] in Amharic

Surah The emissaries [Al-Mursalat] Ayah 50 Location Maccah Number 77

وَٱلْمُرْسَلَٰتِ عُرْفًۭا ﴿١﴾

ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣

فَٱلْعَٰصِفَٰتِ عَصْفًۭا ﴿٢﴾

በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣

وَٱلنَّٰشِرَٰتِ نَشْرًۭا ﴿٣﴾

መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣

فَٱلْفَٰرِقَٰتِ فَرْقًۭا ﴿٤﴾

መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣

فَٱلْمُلْقِيَٰتِ ذِكْرًا ﴿٥﴾

መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣

عُذْرًا أَوْ نُذْرًا ﴿٦﴾

ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡

إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَوَٰقِعٌۭ ﴿٧﴾

ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡

فَإِذَا ٱلنُّجُومُ طُمِسَتْ ﴿٨﴾

ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡

وَإِذَا ٱلسَّمَآءُ فُرِجَتْ ﴿٩﴾

ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡

وَإِذَا ٱلْجِبَالُ نُسِفَتْ ﴿١٠﴾

ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡

وَإِذَا ٱلرُّسُلُ أُقِّتَتْ ﴿١١﴾

መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡

لِأَىِّ يَوْمٍ أُجِّلَتْ ﴿١٢﴾

ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤

لِيَوْمِ ٱلْفَصْلِ ﴿١٣﴾

ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡

وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا يَوْمُ ٱلْفَصْلِ ﴿١٤﴾

የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ ﴿١٥﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

أَلَمْ نُهْلِكِ ٱلْأَوَّلِينَ ﴿١٦﴾

የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?

ثُمَّ نُتْبِعُهُمُ ٱلْءَاخِرِينَ ﴿١٧﴾

ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡

كَذَٰلِكَ نَفْعَلُ بِٱلْمُجْرِمِينَ ﴿١٨﴾

በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ ﴿١٩﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

أَلَمْ نَخْلُقكُّم مِّن مَّآءٍۢ مَّهِينٍۢ ﴿٢٠﴾

ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?

فَجَعَلْنَٰهُ فِى قَرَارٍۢ مَّكِينٍ ﴿٢١﴾

በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡

إِلَىٰ قَدَرٍۢ مَّعْلُومٍۢ ﴿٢٢﴾

እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም

فَقَدَرْنَا فَنِعْمَ ٱلْقَٰدِرُونَ ﴿٢٣﴾

መጣኞች ነን!

وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ ﴿٢٤﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

أَلَمْ نَجْعَلِ ٱلْأَرْضَ كِفَاتًا ﴿٢٥﴾

ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?

أَحْيَآءًۭ وَأَمْوَٰتًۭا ﴿٢٦﴾

ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡

وَجَعَلْنَا فِيهَا رَوَٰسِىَ شَٰمِخَٰتٍۢ وَأَسْقَيْنَٰكُم مَّآءًۭ فُرَاتًۭا ﴿٢٧﴾

በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡

وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ ﴿٢٨﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ٱنطَلِقُوٓا۟ إِلَىٰ مَا كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ ﴿٢٩﴾

«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡

ٱنطَلِقُوٓا۟ إِلَىٰ ظِلٍّۢ ذِى ثَلَٰثِ شُعَبٍۢ ﴿٣٠﴾

«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡

لَّا ظَلِيلٍۢ وَلَا يُغْنِى مِنَ ٱللَّهَبِ ﴿٣١﴾

አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡

إِنَّهَا تَرْمِى بِشَرَرٍۢ كَٱلْقَصْرِ ﴿٣٢﴾

እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡

كَأَنَّهُۥ جِمَٰلَتٌۭ صُفْرٌۭ ﴿٣٣﴾

(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡

وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ ﴿٣٤﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

هَٰذَا يَوْمُ لَا يَنطِقُونَ ﴿٣٥﴾

ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡

وَلَا يُؤْذَنُ لَهُمْ فَيَعْتَذِرُونَ ﴿٣٦﴾

ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡

وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ ﴿٣٧﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

هَٰذَا يَوْمُ ٱلْفَصْلِ ۖ جَمَعْنَٰكُمْ وَٱلْأَوَّلِينَ ﴿٣٨﴾

ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡

فَإِن كَانَ لَكُمْ كَيْدٌۭ فَكِيدُونِ ﴿٣٩﴾

ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡

وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ ﴿٤٠﴾

ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

إِنَّ ٱلْمُتَّقِينَ فِى ظِلَٰلٍۢ وَعُيُونٍۢ ﴿٤١﴾

ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡

وَفَوَٰكِهَ مِمَّا يَشْتَهُونَ ﴿٤٢﴾

ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡

كُلُوا۟ وَٱشْرَبُوا۟ هَنِيٓـًٔۢا بِمَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ ﴿٤٣﴾

«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِى ٱلْمُحْسِنِينَ ﴿٤٤﴾

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ ﴿٤٥﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

كُلُوا۟ وَتَمَتَّعُوا۟ قَلِيلًا إِنَّكُم مُّجْرِمُونَ ﴿٤٦﴾

ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡

وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ ﴿٤٧﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ٱرْكَعُوا۟ لَا يَرْكَعُونَ ﴿٤٨﴾

«ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡

وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ ﴿٤٩﴾

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

فَبِأَىِّ حَدِيثٍۭ بَعْدَهُۥ يُؤْمِنُونَ ﴿٥٠﴾

ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?