Main pages

Surah Those who drag forth [An-Naziat] in Amharic

Surah Those who drag forth [An-Naziat] Ayah 46 Location Maccah Number 79

وَٱلنَّٰزِعَٰتِ غَرْقًۭا ﴿١﴾

በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤

وَٱلنَّٰشِطَٰتِ نَشْطًۭا ﴿٢﴾

በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤

وَٱلسَّٰبِحَٰتِ سَبْحًۭا ﴿٣﴾

መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤

فَٱلسَّٰبِقَٰتِ سَبْقًۭا ﴿٤﴾

መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤

فَٱلْمُدَبِّرَٰتِ أَمْرًۭا ﴿٥﴾

ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

يَوْمَ تَرْجُفُ ٱلرَّاجِفَةُ ﴿٦﴾

ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤

تَتْبَعُهَا ٱلرَّادِفَةُ ﴿٧﴾

ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

قُلُوبٌۭ يَوْمَئِذٍۢ وَاجِفَةٌ ﴿٨﴾

በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡

أَبْصَٰرُهَا خَٰشِعَةٌۭ ﴿٩﴾

ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡

يَقُولُونَ أَءِنَّا لَمَرْدُودُونَ فِى ٱلْحَافِرَةِ ﴿١٠﴾

«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡

أَءِذَا كُنَّا عِظَٰمًۭا نَّخِرَةًۭ ﴿١١﴾

«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»

قَالُوا۟ تِلْكَ إِذًۭا كَرَّةٌ خَاسِرَةٌۭ ﴿١٢﴾

«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡

فَإِنَّمَا هِىَ زَجْرَةٌۭ وَٰحِدَةٌۭ ﴿١٣﴾

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡

فَإِذَا هُم بِٱلسَّاهِرَةِ ﴿١٤﴾

ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡

هَلْ أَتَىٰكَ حَدِيثُ مُوسَىٰٓ ﴿١٥﴾

የሙሳ ወሬ መጣልህን?

إِذْ نَادَىٰهُ رَبُّهُۥ بِٱلْوَادِ ٱلْمُقَدَّسِ طُوًى ﴿١٦﴾

ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤

ٱذْهَبْ إِلَىٰ فِرْعَوْنَ إِنَّهُۥ طَغَىٰ ﴿١٧﴾

ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡

فَقُلْ هَل لَّكَ إِلَىٰٓ أَن تَزَكَّىٰ ﴿١٨﴾

በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»

وَأَهْدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخْشَىٰ ﴿١٩﴾

«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡

فَأَرَىٰهُ ٱلْءَايَةَ ٱلْكُبْرَىٰ ﴿٢٠﴾

ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡

فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ ﴿٢١﴾

አስተባበለም፤ አመጸም፡፡

ثُمَّ أَدْبَرَ يَسْعَىٰ ﴿٢٢﴾

ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡

فَحَشَرَ فَنَادَىٰ ﴿٢٣﴾

(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡

فَقَالَ أَنَا۠ رَبُّكُمُ ٱلْأَعْلَىٰ ﴿٢٤﴾

አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»

فَأَخَذَهُ ٱللَّهُ نَكَالَ ٱلْءَاخِرَةِ وَٱلْأُولَىٰٓ ﴿٢٥﴾

አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡

إِنَّ فِى ذَٰلِكَ لَعِبْرَةًۭ لِّمَن يَخْشَىٰٓ ﴿٢٦﴾

በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡

ءَأَنتُمْ أَشَدُّ خَلْقًا أَمِ ٱلسَّمَآءُ ۚ بَنَىٰهَا ﴿٢٧﴾

ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡

رَفَعَ سَمْكَهَا فَسَوَّىٰهَا ﴿٢٨﴾

ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡

وَأَغْطَشَ لَيْلَهَا وَأَخْرَجَ ضُحَىٰهَا ﴿٢٩﴾

ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡

وَٱلْأَرْضَ بَعْدَ ذَٰلِكَ دَحَىٰهَآ ﴿٣٠﴾

ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡

أَخْرَجَ مِنْهَا مَآءَهَا وَمَرْعَىٰهَا ﴿٣١﴾

ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡

وَٱلْجِبَالَ أَرْسَىٰهَا ﴿٣٢﴾

ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡

مَتَٰعًۭا لَّكُمْ وَلِأَنْعَٰمِكُمْ ﴿٣٣﴾

ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡

فَإِذَا جَآءَتِ ٱلطَّآمَّةُ ٱلْكُبْرَىٰ ﴿٣٤﴾

ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣

يَوْمَ يَتَذَكَّرُ ٱلْإِنسَٰنُ مَا سَعَىٰ ﴿٣٥﴾

ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣

وَبُرِّزَتِ ٱلْجَحِيمُ لِمَن يَرَىٰ ﴿٣٦﴾

ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣

فَأَمَّا مَن طَغَىٰ ﴿٣٧﴾

የካደ ሰውማ፣

وَءَاثَرَ ٱلْحَيَوٰةَ ٱلدُّنْيَا ﴿٣٨﴾

ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣

فَإِنَّ ٱلْجَحِيمَ هِىَ ٱلْمَأْوَىٰ ﴿٣٩﴾

ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

وَأَمَّا مَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِۦ وَنَهَى ٱلنَّفْسَ عَنِ ٱلْهَوَىٰ ﴿٤٠﴾

በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ

فَإِنَّ ٱلْجَنَّةَ هِىَ ٱلْمَأْوَىٰ ﴿٤١﴾

ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

يَسْـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلسَّاعَةِ أَيَّانَ مُرْسَىٰهَا ﴿٤٢﴾

«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡

فِيمَ أَنتَ مِن ذِكْرَىٰهَآ ﴿٤٣﴾

አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?

إِلَىٰ رَبِّكَ مُنتَهَىٰهَآ ﴿٤٤﴾

(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

إِنَّمَآ أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخْشَىٰهَا ﴿٤٥﴾

አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡

كَأَنَّهُمْ يَوْمَ يَرَوْنَهَا لَمْ يَلْبَثُوٓا۟ إِلَّا عَشِيَّةً أَوْ ضُحَىٰهَا ﴿٤٦﴾

እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡