Main pages

Surah The Cleaving [AL-Infitar] in Amharic

Surah The Cleaving [AL-Infitar] Ayah 19 Location Maccah Number 82

إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنفَطَرَتْ ﴿١﴾

ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلْكَوَاكِبُ ٱنتَثَرَتْ ﴿٢﴾

ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلْبِحَارُ فُجِّرَتْ ﴿٣﴾

ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤

وَإِذَا ٱلْقُبُورُ بُعْثِرَتْ ﴿٤﴾

መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤

عَلِمَتْ نَفْسٌۭ مَّا قَدَّمَتْ وَأَخَّرَتْ ﴿٥﴾

ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡

يَٰٓأَيُّهَا ٱلْإِنسَٰنُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ ٱلْكَرِيمِ ﴿٦﴾

አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?

ٱلَّذِى خَلَقَكَ فَسَوَّىٰكَ فَعَدَلَكَ ﴿٧﴾

በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡

فِىٓ أَىِّ صُورَةٍۢ مَّا شَآءَ رَكَّبَكَ ﴿٨﴾

በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡

كَلَّا بَلْ تُكَذِّبُونَ بِٱلدِّينِ ﴿٩﴾

ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡

وَإِنَّ عَلَيْكُمْ لَحَٰفِظِينَ ﴿١٠﴾

በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤

كِرَامًۭا كَٰتِبِينَ ﴿١١﴾

የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡

يَعْلَمُونَ مَا تَفْعَلُونَ ﴿١٢﴾

የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡

إِنَّ ٱلْأَبْرَارَ لَفِى نَعِيمٍۢ ﴿١٣﴾

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡

وَإِنَّ ٱلْفُجَّارَ لَفِى جَحِيمٍۢ ﴿١٤﴾

ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡

يَصْلَوْنَهَا يَوْمَ ٱلدِّينِ ﴿١٥﴾

በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡

وَمَا هُمْ عَنْهَا بِغَآئِبِينَ ﴿١٦﴾

እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡

وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا يَوْمُ ٱلدِّينِ ﴿١٧﴾

የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

ثُمَّ مَآ أَدْرَىٰكَ مَا يَوْمُ ٱلدِّينِ ﴿١٨﴾

ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

يَوْمَ لَا تَمْلِكُ نَفْسٌۭ لِّنَفْسٍۢ شَيْـًۭٔا ۖ وَٱلْأَمْرُ يَوْمَئِذٍۢ لِّلَّهِ ﴿١٩﴾

(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡