Main pages

Surah The morning star [At-Tariq] in Amharic

Surah The morning star [At-Tariq] Ayah 17 Location Maccah Number 86

وَٱلسَّمَآءِ وَٱلطَّارِقِ ﴿١﴾

በሰማዩ በሌሊት መጪውም እምላለሁ፡፡

وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا ٱلطَّارِقُ ﴿٢﴾

የሌሊት መጪውም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?

ٱلنَّجْمُ ٱلثَّاقِبُ ﴿٣﴾

ጨለማን ቀዳጁ ኮከብ ነው፡፡

إِن كُلُّ نَفْسٍۢ لَّمَّا عَلَيْهَا حَافِظٌۭ ﴿٤﴾

ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡

فَلْيَنظُرِ ٱلْإِنسَٰنُ مِمَّ خُلِقَ ﴿٥﴾

ሰውም ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፡፡

خُلِقَ مِن مَّآءٍۢ دَافِقٍۢ ﴿٦﴾

ከተስፈንጣሪ ውሃ ተፈጠረ፡፡

يَخْرُجُ مِنۢ بَيْنِ ٱلصُّلْبِ وَٱلتَّرَآئِبِ ﴿٧﴾

ከጀርባና ከእርግብግብቶች መካከል የሚወጣ ከኾነ (ውሃ)፡፡

إِنَّهُۥ عَلَىٰ رَجْعِهِۦ لَقَادِرٌۭ ﴿٨﴾

እርሱ (አላህ) በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው፡፡

يَوْمَ تُبْلَى ٱلسَّرَآئِرُ ﴿٩﴾

ምስጢሮች በሚገለጡበት ቀን፡፡

فَمَا لَهُۥ مِن قُوَّةٍۢ وَلَا نَاصِرٍۢ ﴿١٠﴾

ለእርሱም (ለሰው) ኀይልና ረዳት ምንም የለውም፡፡

وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلرَّجْعِ ﴿١١﴾

የመመለስ ባለቤት በኾነችው ሰማይም እምላለሁ፡፡

وَٱلْأَرْضِ ذَاتِ ٱلصَّدْعِ ﴿١٢﴾

(በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በኾነችው ምድርም፤

إِنَّهُۥ لَقَوْلٌۭ فَصْلٌۭ ﴿١٣﴾

እርሱ (እውነትን ከውሸት) የሚለይ ቃል ነው፡፡

وَمَا هُوَ بِٱلْهَزْلِ ﴿١٤﴾

እርሱም ቀልድ አይደለም፡፡

إِنَّهُمْ يَكِيدُونَ كَيْدًۭا ﴿١٥﴾

እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ይሠራሉ፡፡

وَأَكِيدُ كَيْدًۭا ﴿١٦﴾

(እኔ) ተንኮልንም እመልሳለሁ፡፡

فَمَهِّلِ ٱلْكَٰفِرِينَ أَمْهِلْهُمْ رُوَيْدًۢا ﴿١٧﴾

ከሓዲዎችንም ቀን ስጣቸው፡፡ ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው፡፡