Main pages

Surah The Most High [Al-Ala] in Amharic

Surah The Most High [Al-Ala] Ayah 19 Location Maccah Number 87

سَبِّحِ ٱسْمَ رَبِّكَ ٱلْأَعْلَى ﴿١﴾

ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡

ٱلَّذِى خَلَقَ فَسَوَّىٰ ﴿٢﴾

የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡

وَٱلَّذِى قَدَّرَ فَهَدَىٰ ﴿٣﴾

የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡

وَٱلَّذِىٓ أَخْرَجَ ٱلْمَرْعَىٰ ﴿٤﴾

የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡

فَجَعَلَهُۥ غُثَآءً أَحْوَىٰ ﴿٥﴾

(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡

سَنُقْرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰٓ ﴿٦﴾

(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡

إِلَّا مَا شَآءَ ٱللَّهُ ۚ إِنَّهُۥ يَعْلَمُ ٱلْجَهْرَ وَمَا يَخْفَىٰ ﴿٧﴾

አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡

وَنُيَسِّرُكَ لِلْيُسْرَىٰ ﴿٨﴾

ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡

فَذَكِّرْ إِن نَّفَعَتِ ٱلذِّكْرَىٰ ﴿٩﴾

ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡

سَيَذَّكَّرُ مَن يَخْشَىٰ ﴿١٠﴾

(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡

وَيَتَجَنَّبُهَا ٱلْأَشْقَى ﴿١١﴾

መናጢውም ይርቃታል፡፡

ٱلَّذِى يَصْلَى ٱلنَّارَ ٱلْكُبْرَىٰ ﴿١٢﴾

ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡

ثُمَّ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحْيَىٰ ﴿١٣﴾

ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡

قَدْ أَفْلَحَ مَن تَزَكَّىٰ ﴿١٤﴾

የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡

وَذَكَرَ ٱسْمَ رَبِّهِۦ فَصَلَّىٰ ﴿١٥﴾

የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡

بَلْ تُؤْثِرُونَ ٱلْحَيَوٰةَ ٱلدُّنْيَا ﴿١٦﴾

ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡

وَٱلْءَاخِرَةُ خَيْرٌۭ وَأَبْقَىٰٓ ﴿١٧﴾

መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡

إِنَّ هَٰذَا لَفِى ٱلصُّحُفِ ٱلْأُولَىٰ ﴿١٨﴾

ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡

صُحُفِ إِبْرَٰهِيمَ وَمُوسَىٰ ﴿١٩﴾

በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡