Main pages

Surah The night [Al-Lail] in Amharic

Surah The night [Al-Lail] Ayah 21 Location Maccah Number 92

وَٱلَّيْلِ إِذَا يَغْشَىٰ ﴿١﴾

በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡

وَٱلنَّهَارِ إِذَا تَجَلَّىٰ ﴿٢﴾

በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡

وَمَا خَلَقَ ٱلذَّكَرَ وَٱلْأُنثَىٰٓ ﴿٣﴾

ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡

إِنَّ سَعْيَكُمْ لَشَتَّىٰ ﴿٤﴾

ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡

فَأَمَّا مَنْ أَعْطَىٰ وَٱتَّقَىٰ ﴿٥﴾

የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡

وَصَدَّقَ بِٱلْحُسْنَىٰ ﴿٦﴾

በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤

فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلْيُسْرَىٰ ﴿٧﴾

ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

وَأَمَّا مَنۢ بَخِلَ وَٱسْتَغْنَىٰ ﴿٨﴾

የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤

وَكَذَّبَ بِٱلْحُسْنَىٰ ﴿٩﴾

በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤

فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلْعُسْرَىٰ ﴿١٠﴾

ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

وَمَا يُغْنِى عَنْهُ مَالُهُۥٓ إِذَا تَرَدَّىٰٓ ﴿١١﴾

በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡

إِنَّ عَلَيْنَا لَلْهُدَىٰ ﴿١٢﴾

ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡

وَإِنَّ لَنَا لَلْءَاخِرَةَ وَٱلْأُولَىٰ ﴿١٣﴾

መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡

فَأَنذَرْتُكُمْ نَارًۭا تَلَظَّىٰ ﴿١٤﴾

የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡

لَا يَصْلَىٰهَآ إِلَّا ٱلْأَشْقَى ﴿١٥﴾

ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡

ٱلَّذِى كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ ﴿١٦﴾

ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡

وَسَيُجَنَّبُهَا ٱلْأَتْقَى ﴿١٧﴾

አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡

ٱلَّذِى يُؤْتِى مَالَهُۥ يَتَزَكَّىٰ ﴿١٨﴾

ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡

وَمَا لِأَحَدٍ عِندَهُۥ مِن نِّعْمَةٍۢ تُجْزَىٰٓ ﴿١٩﴾

ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡

إِلَّا ٱبْتِغَآءَ وَجْهِ رَبِّهِ ٱلْأَعْلَىٰ ﴿٢٠﴾

ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡

وَلَسَوْفَ يَرْضَىٰ ﴿٢١﴾

ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡