Main pages

Surah The morning hours [Ad-Dhuha] in Amharic

Surah The morning hours [Ad-Dhuha] Ayah 11 Location Maccah Number 93

وَٱلضُّحَىٰ ﴿١﴾

በረፋዱ እምላለሁ፡፡

وَٱلَّيْلِ إِذَا سَجَىٰ ﴿٢﴾

በሌሊቱም ጸጥ ባለ ጊዜ፤

مَا وَدَّعَكَ رَبُّكَ وَمَا قَلَىٰ ﴿٣﴾

ጌታህ አላሰናበተህም፤ አልጠላህምም፡፡

وَلَلْءَاخِرَةُ خَيْرٌۭ لَّكَ مِنَ ٱلْأُولَىٰ ﴿٤﴾

መጨረሻይቱም (ዓለም) ከመጀመሪያይቱ ይልቅ ላንተ በላጭ ናት፡፡

وَلَسَوْفَ يُعْطِيكَ رَبُّكَ فَتَرْضَىٰٓ ﴿٥﴾

ጌታህም ወደ ፊት (ብዙን ስጦታ) በእርግጥ ይሰጥሃል፡፡ ትደሰታለህም፡፡

أَلَمْ يَجِدْكَ يَتِيمًۭا فَـَٔاوَىٰ ﴿٦﴾

የቲም ኾነህ አላገኘህምና አላስጠጋህምን? (አስጠግቶሃል)፡፡

وَوَجَدَكَ ضَآلًّۭا فَهَدَىٰ ﴿٧﴾

የሳትክም ኾነህ አገኘህ መራህም፡፡

وَوَجَدَكَ عَآئِلًۭا فَأَغْنَىٰ ﴿٨﴾

ድኻም ኾነህ አገኘህ፤ አከበረህም፡፡

فَأَمَّا ٱلْيَتِيمَ فَلَا تَقْهَرْ ﴿٩﴾

የቲምንማ አትጨቁን፡፡

وَأَمَّا ٱلسَّآئِلَ فَلَا تَنْهَرْ ﴿١٠﴾

ለማኝንም አትገላምጥ፡፡

وَأَمَّا بِنِعْمَةِ رَبِّكَ فَحَدِّثْ ﴿١١﴾

በጌታህም ጸጋ አውራ፤ (ግለጻት)፡፡