Main pages

Surah The Fig [At-Tin] in Amharic

Surah The Fig [At-Tin] Ayah 8 Location Maccah Number 95

بِّسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ وَٱلتِّينِ وَٱلزَّيْتُونِ ﴿١﴾

በበለስና በዘይት ወይራ እምላለሁ፡፡

وَطُورِ سِينِينَ ﴿٢﴾

በሲኒን ተራራም፤

وَهَٰذَا ٱلْبَلَدِ ٱلْأَمِينِ ﴿٣﴾

በዚህ በጸጥተኛው አገርም (እምላለሁ)፡፡

لَقَدْ خَلَقْنَا ٱلْإِنسَٰنَ فِىٓ أَحْسَنِ تَقْوِيمٍۢ ﴿٤﴾

ሰውን በጣም በአማረ አቋም ላይ ፈጠርነው፡፡

ثُمَّ رَدَدْنَٰهُ أَسْفَلَ سَٰفِلِينَ ﴿٥﴾

ከዚያም (ከፊሉን) ከዝቅተኞች ሁሉ በታች አድርገን መለስነው፡፡

إِلَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ وَعَمِلُوا۟ ٱلصَّٰلِحَٰتِ فَلَهُمْ أَجْرٌ غَيْرُ مَمْنُونٍۢ ﴿٦﴾

ግን እነዚያ ያመኑት መልካሞችንም የሠሩት ለእነርሱ ተቆራጭ ያልኾነ ምንዳ አልላቸው፡፡

فَمَا يُكَذِّبُكَ بَعْدُ بِٱلدِّينِ ﴿٧﴾

ታዲያ ከዚህ በኋላ በፍርዱ ምን አስተባባይ አደረገህ?

أَلَيْسَ ٱللَّهُ بِأَحْكَمِ ٱلْحَٰكِمِينَ ﴿٨﴾

አላህ ከፈራጆች ሁሉ ይበልጥ ፈራጅ አይደለምን? (ነው)፡፡