Settings
Surah The City [Al-Balad] in Amharic
لَاۤ أُقۡسِمُ بِهَـٰذَا ٱلۡبَلَدِ ﴿1﴾
በዚህ አገር (በመካ) እምላለሁ፡፡
وَأَنتَ حِلُّۢ بِهَـٰذَا ٱلۡبَلَدِ ﴿2﴾
አንተ በዚህ አገር ሰፋሪ ስትኾን፡፡
وَوَالِدࣲ وَمَا وَلَدَ ﴿3﴾
በወላጂም በወለዳቸውም ሰዎች (በአዳምና በዘሮቹ ሁሉ እምላለሁ)፡፡
لَقَدۡ خَلَقۡنَا ٱلۡإِنسَـٰنَ فِی كَبَدٍ ﴿4﴾
ሰውን ሁሉ በእርግጥ በልፋት ውስጥ ኾኖ ፈጠርነው፡፡
أَیَحۡسَبُ أَن لَّن یَقۡدِرَ عَلَیۡهِ أَحَدࣱ ﴿5﴾
በእርሱ ላይ አንድም የማይችል መኾኑን ይጠረጥራልን?
یَقُولُ أَهۡلَكۡتُ مَالࣰا لُّبَدًا ﴿6﴾
«ብዙን ገንዘብ አጠፋሁ» ይላል፡፡
أَیَحۡسَبُ أَن لَّمۡ یَرَهُۥۤ أَحَدٌ ﴿7﴾
አንድም ያላየው መኾኑን ያስባልን?
أَلَمۡ نَجۡعَل لَّهُۥ عَیۡنَیۡنِ ﴿8﴾
ለእርሱ ሁለት ዓይኖችን አላደረግንለትምን?
وَلِسَانࣰا وَشَفَتَیۡنِ ﴿9﴾
ምላስንና ሁለት ከንፈሮችንም፡፡
وَهَدَیۡنَـٰهُ ٱلنَّجۡدَیۡنِ ﴿10﴾
ሁለትን መንገዶችም አልመራነውምን?
فَلَا ٱقۡتَحَمَ ٱلۡعَقَبَةَ ﴿11﴾
ዓቀበቲቱንም አልወጣም፡፡
وَمَاۤ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡعَقَبَةُ ﴿12﴾
ዓቀበቲቱም (መውጣቷ) ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
فَكُّ رَقَبَةٍ ﴿13﴾
(እርሱ) ጫንቃን መልቀቅ ነው፡፡
أَوۡ إِطۡعَـٰمࣱ فِی یَوۡمࣲ ذِی مَسۡغَبَةࣲ ﴿14﴾
ወይም የረኃብ ባለቤት በኾነ ቀን ማብላት፡፡
یَتِیمࣰا ذَا مَقۡرَبَةٍ ﴿15﴾
የዝምድና ባለቤት የኾነን የቲም፤
أَوۡ مِسۡكِینࣰا ذَا مَتۡرَبَةࣲ ﴿16﴾
ወይም የዐፈር ባለቤት የኾነን ድኻ (ማብላት ነው)፡፡
ثُمَّ كَانَ مِنَ ٱلَّذِینَ ءَامَنُوا۟ وَتَوَاصَوۡا۟ بِٱلصَّبۡرِ وَتَوَاصَوۡا۟ بِٱلۡمَرۡحَمَةِ ﴿17﴾
(ዐቀበቲቱን አልወጣም)፡፡ ከዚያም ከነዚያ ከአመኑትና በመታገስ አደራ ከተባባሉት፣ በማዘንም አደራ ከተባባሉት ሰዎች አልኾነም፡፡
أُو۟لَـٰۤىِٕكَ أَصۡحَـٰبُ ٱلۡمَیۡمَنَةِ ﴿18﴾
እነዚያ (ይህንን የፈጸሙ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
وَٱلَّذِینَ كَفَرُوا۟ بِـَٔایَـٰتِنَا هُمۡ أَصۡحَـٰبُ ٱلۡمَشۡـَٔمَةِ ﴿19﴾
እነዚያም በአንቀጾቻችን የካዱት እነርሱ የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
عَلَیۡهِمۡ نَارࣱ مُّؤۡصَدَةُۢ ﴿20﴾
በእነርሱ ላይ የተዘጋች እሳት አልለች፡፡
 English
 English Chinese
 Chinese Spanish
 Spanish Portuguese
 Portuguese Russian
 Russian Japanese
 Japanese French
 French German
 German Italian
 Italian Hindi
 Hindi Korean
 Korean Indonesian
 Indonesian Bengali
 Bengali Albanian
 Albanian Bosnian
 Bosnian Dutch
 Dutch Malayalam
 Malayalam Romanian
 Romanian