Settings
Surah The Sun [Ash-Shams] in Amharic
وَٱلشَّمۡسِ وَضُحَىٰهَا ﴿1﴾
በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡
وَٱلۡقَمَرِ إِذَا تَلَىٰهَا ﴿2﴾
በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤
وَٱلنَّهَارِ إِذَا جَلَّىٰهَا ﴿3﴾
በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤
وَٱلَّیۡلِ إِذَا یَغۡشَىٰهَا ﴿4﴾
በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤
وَٱلسَّمَاۤءِ وَمَا بَنَىٰهَا ﴿5﴾
በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤
وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا طَحَىٰهَا ﴿6﴾
በምድሪቱም በዘረጋትም፤
وَنَفۡسࣲ وَمَا سَوَّىٰهَا ﴿7﴾
በነፍስም ባስተካከላትም፤
فَأَلۡهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقۡوَىٰهَا ﴿8﴾
አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡
قَدۡ أَفۡلَحَ مَن زَكَّىٰهَا ﴿9﴾
(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡
وَقَدۡ خَابَ مَن دَسَّىٰهَا ﴿10﴾
(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡
كَذَّبَتۡ ثَمُودُ بِطَغۡوَىٰهَاۤ ﴿11﴾
ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡
إِذِ ٱنۢبَعَثَ أَشۡقَىٰهَا ﴿12﴾
ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡
فَقَالَ لَهُمۡ رَسُولُ ٱللَّهِ نَاقَةَ ٱللَّهِ وَسُقۡیَـٰهَا ﴿13﴾
ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡
فَكَذَّبُوهُ فَعَقَرُوهَا فَدَمۡدَمَ عَلَیۡهِمۡ رَبُّهُم بِذَنۢبِهِمۡ فَسَوَّىٰهَا ﴿14﴾
አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡
وَلَا یَخَافُ عُقۡبَـٰهَا ﴿15﴾
ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አያፈራም፡፡
English
Chinese
Spanish
Portuguese
Russian
Japanese
French
German
Italian
Hindi
Korean
Indonesian
Bengali
Albanian
Bosnian
Dutch
Malayalam
Romanian